የስግድ በዓል ከእግዚአብሔር ጋር ቃል ኪዳን የተገባበትን ያስታዉሳል ፡፡ እያናዳናዱ ቤተ እስራኤል የሆነ ሁሉ ልቡን ወደ ፈጣሪ እዙሮ እጸለየ ስለ እየሩሳሌም ጽኑ የሆነ ምኞቱንና ጉጉቱን የሚገልጽበት ቀን ነው ፡፡
የሥግድ በዓል ለኢትዮጵያ ይሁዲወች ልዩ ቦታ አለው ፤ በዚህ ቀን ቤተ እስራኤሎች የራሳቸውን ሃይማኖታዊ፤ መንፈሳዊና ማህበረ ሰባዊ አንድነታቸውን የሚያጠናክሩበት ቀን ነው፡፡
ሥግድ የሚለው ስም " መስገድ " ከሚል ቃል የተወሰደ ሲሆን ፤ ከሴም ቋንቋ ቃል የተወሰደ ፤ ጎንበስ ብሎ መስገድ ማለት ነው ፡፡ ስለሆነም በሥግድ በዓል ቀን ይህ ቃል ለዩ የሆነ ይዘት አለው፤" ለእግዚአብሔር ጎንበስ" ማለት " ምሕለላ" ተብሎም ይጠራል፤ (ይቅር በለኝ ብሎ ፈጣሪን መማጸን) ፡፡ "
የባዓሉ መነሻ ይሁዲወች ከባቢሎን ሥደት ወደ ጺዮን ሲመለሱ በመጽሃፈ ዕዝራና ነሀሚያ እንደሚተረከው ሕዝቡ ወደ ህይማኖቱ ተመልሶ የእግዚብሔር አገልጋይ እንዲሆን ጉባኤ ተደርጎ የተመከረበት ቀን ነው፡፡" ዕዝራ ከሕዝቡ ከፍ ብሎ በተሠራው መድረክ ላይ በቆመ ጊዜ ሁሉም ትኩር ብለው ይመለከቱት ነበር ፤እርሱም የሕጉን መጽሐፍ በከፈተ ጊዜ ሕዝቡ ሁሉ ከተቀመጠበት ተነሣ ፡፡ ዕዝራም " ታላቅ አምላክ የሆነ እግዚአብሔር ይመስገን " አለ ፡፡ ሕዝቡም ሁሉ እጃቸውን ወደ ላይ በማንሣት " አሜን አሜን " ሲሉ መለሱ ወደ ምድርም ለጥ ብለው ፊታቸውን መሬት በማስነካት ለእግዚአብሔር ሰገዱ ፡፡ ከዚህ በኋላ ተነስተው ባሉበት ስፍራ ቆሙ ፡፡ ከዚህ ቀጥሎ ስማቸው የተዘረዘረ ሌዋውያንም የሕጉን መጽሐፍ ትርጉም ለሕዝቡ ገለጡላቸው ፡፡ እነርሱም ፤ ኢያሱ ፤ ባኒ ሼሬብያ ፤ ቀሊጣ ፤ ዐዛሪያ ፤ ዮዛባድ ፤ ሐናንና ፐልያ ነበሩ ፡፡
ያለፉት አጋጣሚዎች

የስግድ በዓል በእየሩሳሌም

የስግድ ጸሎት በእየሩሳሌም
