ወደ እስራኤል (እየሩሳለም) ለመምጣት በመንገድ ላይ ሳሉ ሕይወታቸው ያልፈ የኢትይጵያ ይሁዲወች የሙታን መታሰቢያ ቀን
ይህ ቀን ሕልማቸውና ምኞታቸው እዉን ሳይሆንላቸው ወደ እየሩሳሌም በመንገድ እያሉና ሱዳን ዉስጥ ሕይወታቸው ያለፈው፤ እሴት ወንድ፤ አዛውንት ፤ ታዳጊ ልጆችና ህጻናት የሚታሰብበት ቀን ነው ፡፡ ይህ ቀን ለኢትጵያ ይሁዲወች በጣም ከባድና የሃዘን ቀን ነው ፤ በተለይ ቤተ ሰብ ለሞተባቸው ፡፡
የሙታን መታሰቢያው ቀን እየሩሳሌም በተዋሃደችበት ቀን እንዲሆን የተወሰነበት ምክያት አለው ፡፡ ከትውልድ እስከ ትውልድ ለብዙ ሽህ ዓመታት ሲያልሟት የኖሩት እየሩሳሌም የተዋሃደችበት ቀን ስለሆነ፤
በዚህ የሙታን መታሰቢያ ቀን የትዮጵያ ይሁዲወች፤ እስራኤል በሚኖሩባቸው ከተሞች ሁሉ ይዘከሩታል ፡፡ትልቁ የሙታን መታሰቢያ ቀን በመንግስታዊ ደረጃ እየሩሳሌም በሃር ሄርጽል ሲሆን ፤ መንግሥታዊ ባለስልጣናት፤ የሙታን ቤተ ሰቦችና ዘመዶች እንዲሁም ሌላ የሥራኢል ህብረተ ሰብ አባላት ይሳተፉበታል፤፡፡
ያለፉት አጋጣሚዎች
May
18
በሱዳን በኩል እሥራኤል ለመግባት በመንገድ ሳሉና ሱዳን ውስጥ የሂዎት ምስዋዕትነት ለከፈሉት ቤተ እሥራኤላውያን ወገኖቻችን በመንግሥት ደረጃ የሚካሄደው የመዘከር ሥነ ሥርዓት የቀጥታ ስርጭት።
18.05.2023
11:00
June
05
እስራኤል ለመድረስ በሱዳን ጉዞ ሞተው ለቀሩት የኢትዮጵያ ይሁዳውያን መንግስታዊ መታሰቢያ ሥነ ሥርዓት የቀጥታ ስርጭት
Herzl's Grave, Mount Herzl Cemetery, Jerusalem
05.06.2024
11:00 - 13:00
May
14
እስራኤል ለመድረስ በሱዳን ጉዞ ሞተው ለቀሩት የኢትዮጵያ ይሁዳውያን መንግስታዊ መታሰቢያ ሥነ ሥርዓት የቀጥታ ስርጭት
Herzl's Grave, Mount Herzl Cemetery, Jerusalem
14.05.2026
11:00 - 13:00
ወደ እስራኤል ለመምጣት ህይወታቸውን ላጡ የኢትዮጵያ ይሁዳውያን የሚደረገው ዓመታዊ እና ሀገራዊ የመንግስት መታሰቢያ ሥነ- ስርዓት፤ ሐሙስ 14.05.2026 ዓ.ም በሃር ሄርጸል እየሩሳሌም፣ ከረፋዱ አስራ አንድ ሰዓት፣ (11:00 ሰዓት) ላይ ይከበራል።