November
13
![የስግድ ጸሎት በእየሩሳሌም](https://ethiopianjhc.org.il/am/wp-content/uploads/sites/3/2023/11/05.jpg)
የስግድ ጸሎት በእየሩሳሌም
በእየሩሳሌም አርሞን ሀናጺቭ መናፈሻ ተራራ
13.11.2023
09:30 - 13:00
አገራችን ባለችበት "የብረት ሰይፎች" ጦርነት ምክንያት እና በደጀን እዝ (ፒኩድ ሀዖሬፍ) መመርያ መሰረት፣
የስግድ ጸሎት በካህናት ተሳትፎ ብቻ በእየሩሳሌም አርሞን ሀናጺቭ መናፈሻ ተራራ ይካሄዳል፡፡
ማህበረሰቡ በየአለበት ቦታ ጸሎቱን እንዲከታተል፣ ከእየሩሳሌም በቀጥታ ስርጭት በኢትዮጵያ ይሁዳውያን
ባህል እና ቅርስ ማእከል ድረ-ገጽ፣ ዩቲዩብ እና ፌስቡክ
ከ 9፡30 እስከ 13፡00 ሰዓት መከታተል ይችላል።
ከጸሎቱ በኋላ የክብር እንግዶች ንግግር አይደረግም፡፡
በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ፣ በኢትዮጵያ ይሁዳውያን ባህል እና ቅርስ ማእከል፣
በካህናት-የሐይማኖት አመራር እና የክብረ በዓላት እና መንግስታዊ ዝግጅቶችን
አቀናባሪ ክፍል ተዘጋጀ
November
23
![የስግድ በዓል በእየሩሳሌም 2022](https://ethiopianjhc.org.il/am/wp-content/uploads/sites/3/2022/11/1840x500.2.png)
የስግድ በዓል በእየሩሳሌም
ቦታውም በኢየሩሳሌም አርሞን ሃናጺብ አጠገብ በሚገኘው ታየሌት ሽሩበር በተባለው መናፈሻ ቦታ ነው
23.11.2022
08:00 - 14:00
በእየሩሳሌም ከተማ በሚካሄደው የስግድ በዓል
ማዕከላዊ የጸሎት ስነ ስርዓት አከባበር እንዲሳተፉ
በአክብሮት ተጋብዘዋል
በዓሉ የሚከበረው ረቡዕ ህዳር(ኖቬምበር)
23 ቀን 2022 ዓ/ም ካፍ-ቴት በሄሽቫን- ታፍ-ሺን-ፔ-ጊሜል ሲሆን
ቦታውም በኢየሩሳሌም አርሞን ሃናጺብ አጠገብ በሚገኘው ታየሌት ሽሩበር በተባለው መናፈሻ ቦታ ነው
የጸሎቱ ስነ ሥራዓት መድረክ በ 8፡00 ሰዓት ይጀምራል
የበዓሉ መንግሥታዊው አከባበር በ12:30 ሰዓት ይካሄዳል
በዚሁ ቀን ከእየሩሳሌም አውቶቡስ ጣቢያ(ታሃና መርካዚት) ዝግጅቱ ወደሚከናወንበት ቦታ የሚወስዱ ልዩ የህዝብ ማጓጓዣዎች ተዘጋጅተዋል:: በተጨማሪም ከመላው ሀገሪቱ ወደ እየሩሳሌም የሚወስዱ አውቶብሶችም ተዘጋጅተዋል::
የአውቶቡሶችን መነሻ ጊዜ እና ቦታ ለማወቅ በአካባቢ ያሉትን መስተዳድሮች በመጠየቅ ወይም የማስታወቂያ ክፍል ቢሮ ድረ ገጽ በማየት ማብራሪያ ማግኘት ይቻላል::
https://www.gov.il/he/departments/hq-for-state-ceremonies-and-events