May
26

እስራኤል ለመድረስ በሱዳን ጉዞ ሞተው ለቀሩት የኢትዮጵያ ይሁዳውያን መንግስታዊ መታሰቢያ ሥነ ሥርዓት የቀጥታ ስርጭት
Herzl's Grave, Mount Herzl Cemetery, Jerusalem
26.05.2025
11:00 - 13:00
November
28

የስግድ በዓል በእየሩሳሌም
በኢየሩሳሌም፣ አርሞን ሃናጺብ አጠገብ በሚገኘው ታየሌት ሽሩበር መናፈሻ ቦታ ነው
28.11.2024
08:00 - 14:00
በእየሩሳሌም ከተማ በሚካሄደው ማዕከላዊ የስግድ ጸሎት ሥነ ሥርዓት አከባበር
እንዲሳተፉ በአክብሮት ተጋብዘዋል
ሐሙስ ቀን 28/11/2024 ካፍ ዛይን በሔሽቫን ታፍ-ሺን-ፔ-ሄይ
በኢየሩሳሌም፣ አርሞን ሃናጺብ አጠገብ በሚገኘው ታየሌት ሽሩበር መናፈሻ ቦታ ነው
በ 8፡00 ሰዓት የጸሎቱ ቦታ ይከፈታል
በ 12፡30 ሰዓት ቡራኬ እና መንግሥታዊው አከባበር
በ 14፡00 የጸሎት እና የፆም መጨረሻ
በዚሁ ቀን ከእየሩሳሌም ሻዛር ጎዳና ቢንያኔ ሃኡማ አጠገብ ወደ ዝግጅቱ ቦታ
የሚያደርሱ የመጓጓዣ አውቶቡሶች ይሰማራሉ።
በተጨማሪም ከመላው ሀገሪቱ ወደ እየሩሳሌም የሚወስዱ አውቶብሶችም ተዘጋጅተዋል::
ለተጨማሪ መረጃ፡
በኢሜል info@moreshete.org.il ስልክ 02-6772568
June
05

እስራኤል ለመድረስ በሱዳን ጉዞ ሞተው ለቀሩት የኢትዮጵያ ይሁዳውያን መንግስታዊ መታሰቢያ ሥነ ሥርዓት የቀጥታ ስርጭት
Herzl's Grave, Mount Herzl Cemetery, Jerusalem
05.06.2024
11:00 - 13:00
April
16

የቤተ እስራኤል የበዓላት ጸሎት መጽሐፍት ምረቃ
16.04.2024
17:00 - 20:00
የኢትዮጵያ ይሁዳውያን ባህል ማዕከል፣ በቤተ እስራኤል የበዓላት ጸሎት መጽሐፍት ምረቃ ይሳተፉ ዘንድ ይጋብዝዎታል
ዕለተ ማክሰኞ ኔሳን 8 ቀን 16.4.2024 በ 17፡00 ሰዓት
ኤሽኮል 2 አዳራሽ ቢንያኔ ሃኡማ ሻዛር ጎዳና ቁ. 1 እየሩሳሌም
በምረቃው ስነሥርዓት ሊቃ ካህናት ብርቁ፣ ቄሶች፣ የሕዝብ ተወካዮች እና ሰፊው ማሕበረሰብ ይገኙበታል።
የበዓላት ጸሎት መጽሐፍት በሁለት ጥራዞች ይከፈላሉ
1 - የአቪቭ ወራት በዓላት፣ የኔሳን፣ ፋሲካ እና የሰኔ ማእረር
2 - የሰባተኛው ወር በዓላት፤ ብርሃን ሠረቀ፣ በዓለ መጸለት እና የህዳር ማእረር
መጽሐፉን አሰባስበው የጻፉት ካህን ምንተስኖት ማሙ ሲሆኑ፣ የኢትዮጵያ ይሁዳውያን ባህል ማዕከል አርሞ ለምረቃ አዘጋጅቷል።
የተሳትፎ ገደብ ስላለው፣ ቅድመ ምዝገባ ያስፈልጋል።
እንጠብቅዎታለን
ዝግጅቱ በካሜራ ይቀረጻል
November
13

የስግድ ጸሎት በእየሩሳሌም
በእየሩሳሌም አርሞን ሀናጺቭ መናፈሻ ተራራ
13.11.2023
09:30 - 13:00
አገራችን ባለችበት "የብረት ሰይፎች" ጦርነት ምክንያት እና በደጀን እዝ (ፒኩድ ሀዖሬፍ) መመርያ መሰረት፣
የስግድ ጸሎት በካህናት ተሳትፎ ብቻ በእየሩሳሌም አርሞን ሀናጺቭ መናፈሻ ተራራ ይካሄዳል፡፡
ማህበረሰቡ በየአለበት ቦታ ጸሎቱን እንዲከታተል፣ ከእየሩሳሌም በቀጥታ ስርጭት በኢትዮጵያ ይሁዳውያን
ባህል እና ቅርስ ማእከል ድረ-ገጽ፣ ዩቲዩብ እና ፌስቡክ
ከ 9፡30 እስከ 13፡00 ሰዓት መከታተል ይችላል።
ከጸሎቱ በኋላ የክብር እንግዶች ንግግር አይደረግም፡፡
በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ፣ በኢትዮጵያ ይሁዳውያን ባህል እና ቅርስ ማእከል፣
በካህናት-የሐይማኖት አመራር እና የክብረ በዓላት እና መንግስታዊ ዝግጅቶችን
አቀናባሪ ክፍል ተዘጋጀ